July 7, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ኢትዮጵያና ኦስትሪያ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ማሳደግ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መከሩ

 የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የኦስትሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ሲሞን ክናፕ ጋር በኢትዮጵያና ኦስትሪያ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል፡፡

አምባሳደር ምስጋኑ የሀገራቱ ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ መስኮች በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

አምባሳደር ክናፕ በበኩላቸው÷ የኦስትሪያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንዲሁም የኦስትሪያ የቢዝነስ ልዑካን ቡድን በመጭው ጥቅምት ወር በኢትዮጵያ ጉብኝት ለማድረግ ያለውን እቅድ አብራርተዋል።

ሁለቱ ወገኖች በኦስትሪያ የንግድ ተቋማት እና በኢትዮጵያውያን አቻዎቻቸው መካከል የልምድ ልውውጥ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን መጠቆማቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ማዕድን ሚኒስቴርንና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን በኦስትሪያ ከሚገኙ የሚመለከታቸው አካላት ጋር በማስተሳሰር በማዕድን ዘርፍ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያንን አቅም ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ላይም ተወያይተዋል።

FBC