ሰኔ 16 ቀን 2016 ሊካሄድ የነበረው 40ኛው የሻንበል አበበ ቢቂላ ማራቶን ውድድር ወደ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም መራዘሙን አትሌቲክስ ፌደሬሽን አስታወቀ፡፡
በተመሳሳይ ከሰኔ 11 እስከ 15 ቀን 2016 ሊካሄድ የነበረው 12ኛው ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሰኔ 25 እስከ 29 ቀን እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡
ውድድሮቹ የሚካሄዱት በሐዋሳ ከተማ መሆኑን የፌደሬሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡
ፌደሬሽኑ ለሁሉም ክልሎች፣ ከተማ አሥተዳደሮች፣ ክለቦች፣ ተቋማት እና የግል ተወዳዳሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት÷ ምዝገባው እስከ ሰኔ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን አስታውቋል፡፡
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።