ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ እና ልማት ዘርፍ ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጸች፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከፊንላንድ የውጭ ንግድና ልማት ሚኒስትር ቪሌ ታቪዮ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷በሀገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና ተያያዥ ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ በትኩረት መክረዋል፡፡
አምባሳደር ምስጋኑ÷ፊላንድ በኢትዮጵያ በተለይም በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ እንድታደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ፊንላንድ ለኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ላደረገችው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውንም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
ቪሌ ታቪዮ በበኩላቸው÷ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድና ልማት ዘርፍ ያላትን ትብብር ይበልጥ እንደምታጠናክር ተናግረዋል፡፡
ሁለቱ ወገኖች በቅርቡ የኢትዮ-ፊላንድ የጋራ የፖለቲካ ምክክር መድረክ ለማካሄድ መስማማታቸውም ተገልጿል፡፡
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።