July 7, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ከ371 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

ከ371 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ ከግንቦት 23 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ነው 128 ሚሊየን ብር የገቢና 243 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር የወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎች የተያዙት፡፡

ከተያዙት እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ቡና፣ መድሃኒት፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች፣ የግንባታ እቃዎች፣ አደንዛዥ እፆችና ሌሎች እቃዎች እንደሚገኙበት ተገልጿል፡፡

በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር አዲስ አበባ ኤርፖርት፣ ሞያሌ እና አዋሽ ቅረንጫፍ ጽ/ቤቶች ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዙ የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡

FBC