ከ371 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ከግንቦት 23 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ነው 128 ሚሊየን ብር የገቢና 243 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር የወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎች የተያዙት፡፡
ከተያዙት እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ቡና፣ መድሃኒት፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች፣ የግንባታ እቃዎች፣ አደንዛዥ እፆችና ሌሎች እቃዎች እንደሚገኙበት ተገልጿል፡፡
በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር አዲስ አበባ ኤርፖርት፣ ሞያሌ እና አዋሽ ቅረንጫፍ ጽ/ቤቶች ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዙ የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
ኢትዮጵያ የፊታችን ነሀሴ በአንካራ በሚካሄደው ድርድር ምን ትጠብቃለች?
የአይቻልም እና የአይሆንም መንፈስን መስበር ከተቻለ የማይቻል ነገር የለም “- ተማሪ ወጋየሁ ወራጆ
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ለምክር ቤቱ ማብራሪያ ይሰጣሉ