የኢራን የሀገርውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ለሀገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የሚወዳደሩ 6 እጩዎችን ይፋ አድርጓል፡፡
ሚኒስቴሩ በዚህ ወር በሚካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የሚወዳደሩ የስድስት እጩዎችን የመጨረሻ ዝርዝር ነው ይፋ ማድረጉ የተሰማው፡፡
ፕሬዚዳንታዊ ምርጫው በቅርቡ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ በሄሊኮፍተር አደጋ ህይዎታቸው ማለፉን ተከትሎ ለሀገሪቱ አዲስ ፕሬዚዳንት መምረጥ በማስፈለጉ ነው የሚካሄደው፡፡
ለፕሬዚዳንትነት ከሚወዳደሩት እጩዎች መካከል በሀገሪቱ በምክትልፕሬዚዳንትነት እያገለገሉ የሚገኙትን አሚርሆሴይን ቃዚዛዴህ ሃሺሚን ን ጨምሮ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች እያገለገሉ ያሉ ሃላፊዎች እንደሚገኙበት የአርቲ ዘገባ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት ጉዳይ ንግግር ለመጀመር አጥጋቢ እቅድ እንዳልደረሳት ገለጸች