July 7, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አየር መንገዱ ወደ ቦትስዋና ማኡን ከተማ በረራ ጀመረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦትስዋና የቱሪስት መዳረሻ ወደ ሆነችው ማኡን ከተማ በረራ ጀመረ።

በማስጀመሪያው መርሐ-ግብር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስጻሚ መስፍን ጣሰው ፣የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ሃላፊ ለማ ያዴቻ በኢትዮጵያ የቦትስዋና አምባሳደር ተብሌሎ አልፈርድ ቦአንግ ተገኝተዋል።

አቶ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት÷ አየር መንገዱ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ መዳረሻውን በየጊዜው እያሰፋ ይገኛል።

አየር መንገዱ አፍሪካንና አፍሪካዊያንን ለማስተሳሰር የያዘውን ውጥን ከግብ ለማድረስ በትጋት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

FBC