በአፋር ክልል ዱብቲ ወረዳ የሚገኙ የጂኦተርማል ፕሮጀክቶችን ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢጃራ ተስፋዬ የተንዳሆ እና አላሎ ባድ የጂኦተርማል ፕሮጀክቶችን ጎብኝተው ፕሮጀክቶቹ ያሉበትን ሁኔታ ተመልክተዋል፡፡የጉብኝቱ ዓላማ ፕሮጀክቶቹ ያሉበትን ችግር ለመፍታትና ወደ ስራ ለማስገባት መሆኑን ከኢንስቲትዩቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡በሚቀጥለው ዓመት ለፕሮጀክቶቹ በጀት በመመድብ ጥገና በማድረግ ወደ ስራ ለማስገባት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነም ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።በተያያዘ በሰመራ ከተማ የሚገኘውን የኢንስቲትዩቱ ንብረቶች ያሉበትን ሁኔታም ተመልክተዋል።
FBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ