172 ፍልሰተኞች ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።ኤምባሲውና የዓለም አቀፍ ፍልሰተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) በትብብር በሦስት ዙር 172 መደበኛ ያልሆኑ ፍልሰተኞችን በዚህ ሣምንት በአውሮፕላንና በባቡር ወደ ሀገራቸው መመለስ መቻሉ ተገልጿል። የኢትዮ-ጅቡቲ-የመን መንገድ እጅግ አደገኛ ከመሆኑም በላይ በድንበር ተሻጋሪ ሕገ-ወጥ ቡድኖች ምክንያት ዜጎች ለድብደባ፣ እንግልት፣ ዘረፋ እንዲሁም ሞት እየተዳረጉ እንደሚገኙ ኤምባሲው ባወጣው መረጃ አስገንዝቧል።ለዚህም ዜጎች ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን ከዚህ መሰል አደጋ ለመጠበቅ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በትብብር በመስራት የጋራ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል።
EBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።