ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተወክለው በምክክር መድረኩ ላይ በመሳተፍ ላይ ለሚገኙ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ መሳተፍ ታላቅ ሃገራዊ ሃላፊነት ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ የመዲናዋ ነዋሪዎች ከማንኛውም የግልና የቡድን ስሜት እና አመለካከት በመውጣት በምክክሩ በንቃት እንዲሳተፉ ጠይቀዋል።
ከንቲባዋ በመልዕክታቸው፥ ለዘመናት ልዩነቶችን በሃይልና በጠመንጃ ከመፍታት ታሪክ በመውጣት በሰለጠነ መንገድ በውይይት ለመፍታት የሚያግዘን ሃገራዊ ምክክር በርዕሰ መዲናችን አዲስ አበባ መጀመሩ ትልቅ ታሪካዊ ክስተት ነው ብለዋል።
እንደ ሃገር ያሉንን በርካታ መልካም ነገሮቻችንን በሚያጠለሽ መልኩ መጥፎ ገፅታችን ከነበረው ልዩነቶችን በጠመንጃ እና በጉልበት ከመፍታት እና የአንድ ሃገር ህዝቦች በዚህ ልክ በጠላትነት ከመፈራረጅ ተላቅቀን ልዩነቶቻችንን በውይይት ብቻ በመፍታት በሃገራችን ዘላቂ ሰላም እንድናሰፍን ምክክሩ ቁልፍ ሚና ይጫወታል ብለዋል።
ይህ ለሃገራችን ተጨማሪ ታሪክና ታላቅ ውጤት የሚያስገኘው ሃገራዊ ምክክር፣ ህዝባችን የስልጣን እና የጉዳዩ ባለቤት በመሆን ራሱ በቀጥታና በመረጣቸው ተወካዮቹ አማካኝነት አጀንዳዎችን አቀራራቢ በሆነ መንገድ በምክክር በመፍታት ሃገራዊ መፍትሄ እንደሚያመጣ ይጠበቃል ነው ያሉት።
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።