የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ከጣሊያን አምባሳደር ኦገስቲኖ ፔልሲ ጋር ተወያይተዋል።
ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው በቱሪዝም ዘርፍ በጣሊያን መንግሥት ትብብር ስለሚከናወኑ ተግባራት ተነጋግረዋል።
አምባሳደር ኦገስቲኖ ፔልሲ፥ የጣሊያን መንግሥት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ለሚያከናውናቸው የቅርስ እድሳት እና የቱሪዝም ልማት ስራዎች የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም በቱሪዝም ዘርፍ የሰው ኃይል ልማት ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት መደረሱን ከቱሪዝም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።