የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ከጣሊያን አምባሳደር ኦገስቲኖ ፔልሲ ጋር ተወያይተዋል።
ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው በቱሪዝም ዘርፍ በጣሊያን መንግሥት ትብብር ስለሚከናወኑ ተግባራት ተነጋግረዋል።
አምባሳደር ኦገስቲኖ ፔልሲ፥ የጣሊያን መንግሥት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ለሚያከናውናቸው የቅርስ እድሳት እና የቱሪዝም ልማት ስራዎች የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም በቱሪዝም ዘርፍ የሰው ኃይል ልማት ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት መደረሱን ከቱሪዝም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖላንድ ሪፐብሊክ ርዕሰ መዲና ዋርሶ አዲስ በረራ ጀመረ
እስራኤል አስራቸው የነበሩትን 55 ፍልስጤማውያን ለቀቀች
የፌዴሬሽን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ