July 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ባርሴሎና እግር ኳስ ክለብ አሰልጣኝ ዣቪ ሄርናንዴስን አሰናበተ

አሰልጣኙ ከወራት በፊት ባርሴሎናን እለቃለሁ ብሎ የነበረ ቢሆንም ውሳኔውን እንደቀየረ አሳውቆ ነበር

ባርሴሎና ጀርማናዊውን ሀንሲ ፍሊክ የዣቪ ተተኪ ለማድረግ ማሰቡ ተገልጾ ነበር

ባርሴሎና አሰልጣኙ ዣቪን አሰናበተ፡፡

የስፔኑ ባርሴሎና እግር ኳስ ክለብ አሰልጣኝ ዣቪ ሄርዳንዴስን አሰናብቷል፡፡

እንደ ቢቢሲ ዘገባ ዣቪ ከወራት በፊት ባርሴሎናን ከዘንድሮው ውድድር መጠናቀቅ በኋላ ክለቡን እንደሚለቅ አሳውቆ ነበር፡፡

ይሁንና ባርሴሎና ከአሰልጣኙ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች ዣቪ በአሰልጣኝነቱ እንዲቀጥል መስማማቱንም አሳውቆ ነበር፡፡

ባርሴሎና ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሰልጣኝ ዣቪ ከአሰልጣኝነት ማሰናበቱን ገልጿል፡፡

የ44 ዓመቱ ዣቪ ላለፉት ሶስት ዓመታት የልጅነት ክለቡን ሲያሰለጥን ቆይቷል፡፡

ባርሴሎና ጀርመናዊውን ሀንሲ ፍሊክ የዣቪ ተተኪ ለማድረግ ውይይቶች በመደረግ ላይ እንደሆኑ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡

አሰልጣኝ ዣቪ በባርሴሎና ቆይታው አንድ የስፔን ላሊጋ ዋንጫ እና ሱፐር ካፕ ዋንጫን ማሸነፍ ችሏል፡፡

Al-Ain