July 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን (EFPApp) ሥራ አስጀመሩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ያከናወናቸው የዲጂታል ሪፎርም ሥራዎች ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ወንጀልን የመከላከል አቅሙን ከፍ የሚያደርጉ መሆናቸውን ገለጹ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ዛሬ አመሻሹን የፌደራል ፖሊስ የዜጎች መረጃ መቀበያ ማዕከልን መርቀው ከፍተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የለማ እና ዜጎች ወንጀልን በቀላሉ ለማዕከሉ የሚጠቁሙበት EFPApp የተሰኘ መተግበሪያንም ስራ አስጀምረዋል።ዲጅታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በርካታ ሥራዎች መከወናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተው፤ በመንግሥታዊ ተቋማት ከ500 በላይ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ መደረጋቸውን ጠቅሰዋል።ፌደራል ፖሊስም በማሻሻያው የዲጂታላይዜሽን አሠራርን በመተግበር ህብረተሰቡ በየትኛውም አካባቢ ሆኖ የወንጀል ድርጊትን መጠቆም የሚችልበትን ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ማድረጉ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርለት ተናግረዋል።ሁሉም ዜጋ መተግበሪያውን በመጠቀም ወንጀልን በጋራ የመከላከል ኃላፊነቱን እንዲወጣም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት አስተላልፈዋል።

EBC