July 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ቻይና በ12 የአሜሪካ ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ ጣለች

ሀገሪቱ ማዕቀቡን የጣለችው ለታይዋን የጦር መሳሪያ አቅርበዋል በሚል ነው

አሜሪካ ከሰሞኑ ለሩሲያ ድጋፍ አድርገዋል በሚል በቻይና ኩባንያዎች ላይ ተመሳሳይ ማዕቀብ ጥላለችቻይና በ12 የአሜሪካ ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ ጣለች።የዓለማችን ቁጥር አንድ እና ሁለት ልዕለ ሀያል ሀገራት አሜሪካ እና ቻይና አንዳቸው በሌላቸው ላይ ማዕቀብ እየጣሉ ይገኛሉ።ከሰሞኑ አሜሪካ በቻይና ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ የጣለች ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ ለሩሲያ ድጋፍ አድርገዋል በሚል ነው።ቻይናም 12 የአሜሪካ ጦር መሳሪያ አምራች ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ በመጣል በዋሽንግተን ለተደረገባት ቅጣት የአጸፋ እርምጃ መውሰዷን አስታውቃለች።እንደ ሮይተርስ ዘገባ ቻይና ዋነኛ የአሜሪካ ጦር መሳሪያ አምራች ኩባንያዎች ለታይዋን ድጋፍ አድርገዋል በሚል ማዕቀብ ጥላለች።ኩባንያዎቹ በተጣለባቸው ማዕቀብ ምክንያት በቻይና ያላቸው ሀብት እንዳይንቀሳቀስ፣ የኩባንያዎቹ አመራሮች ቻይናን እንዳይጎበኙ እና ከቻይናዊያን ጋር ግብይት እንዳይፈጽሙ ታግደዋል።በቻይና ማዕቀብ ከተቀጡ የአሜሪካ ጦር መሳሪያ እምራች ኩባንያዎች መካከል ሎክሂድ ማርቲን፣ ጀነራል ዳይናሚክስ እና ራይቲዮን ዋነኞቹ ናቸው።የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በዩክሬን ጦርነት ገለልተኛ መሆኑን በአንጻሩ አሜሪካ ግን ፍጹም ለዩክሬን እየደገፈች እንደሆነ ይህም ዘላቂ ሰላም እንደማያመጣ አስታውቋል።

Al-Ain