July 7, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

1 ሺህ 175 ኢትዮጵያውያን ከሳውዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

በዛሬው ዕለት በ3 ዙር በረራ በተከናወነ በሳውዲ አረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎችን የመመለስ ስራ፣ 1 ሺህ 175 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ ተችሏል።

ወደ ሀገር የተመለሱት 1 ሺህ 175 ዜጎች ሁሉም ወንዶች ሲሆኑ፤ ከተመላሾች መካከል 18 ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊ ህጻናት ይገኙበታል።

ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ መሆኑን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

ከሚያዚያ 04 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ፣ እስካሁን ከ27 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉ ተገልጿል።

EBC