በ16 ተሽከርካሪ ወደ መሀል ሀገር ሊገቡ የተዘጋጁ 525 ሚሊየን 245 ሺህ ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በትናንትናው ዕለት በሶማሌ ክልል ቢዮባሃይ በተባለ አካባቢ ተያዙ፡፡
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ ሊያዙ የቻሉት የሶማሌ ክልል መንግሥት የፀጥታ አካላት፣ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስ ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ከተያዙት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መካከልም አልባሳት፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ መድኃኒት፣ ሲጋራ፣ የቤት ክዳን ቆርቆሮ እና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡
በድርጊቱ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የክትትል ሥራዎች ተጠናክረው መቀጣላቸውን የጉምሩክ ኮሚሽን መረጃ አመላክቷል፡፡
EBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።