የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ፎረም “ከፍተኛ ትምህርት ለላቀ ውጤት” በሚል መሪ ሀሳብ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ይገኛል።ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ፎረም ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሸኔ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ለማሻሻል የተለያዩ ተግባራት እየተከናኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል።ሚኒስትር ዴኤታው፤ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት መስቀለኛ መንገድ ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል።የጥራት፣ የመልካም አስተዳደር እና የገንዘብ ድጋፍ ችግሮች ተቋማቱን እየፈተ ስለመሆኑ ነው የጠቆሙት።የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ለማሻሻል የሪፎርም ስራዎች እየተተገበረ መሆኑን ገልጸው፤የትምህርት ስርዓቱን ለመቀየር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም አንስተዋል።
EBC
More Stories
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ለምክር ቤቱ ማብራሪያ ይሰጣሉ
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ኢትዮጵያና ዑጋንዳ በቀጣናው ሰላምና ፀጥታን በማስፈን ረገድ ጉልህ ሚና አላቸው አሉ
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በኮምቦልቻ ከተማ ተጀመረ