ክልላዊ ራዕይ እውን ለማድረግ የተግባርና የአስተሳሰብ አንድነት በመፍጠር የህዝባችንን ጥያቄ መፍታት የሚያስችል አሰራር ለመፍጠር እየሰራን ነው ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ፡፡የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የከፍተኛ አመራሮች መድረክ “የክልላችን ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለራዕያችን ስኬት” በሚል መሪ ሀሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ነው።ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረክ እንደገለጹት ÷መድረኩ በክልሉ፣ በብልፅግና ፓርቲና በመንግስት የተከናወኑ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም መነሻ በማድረግ ወቅታዊ ሁኔታ በሚገባ ተረድቶ በቀጣይ የህዝቡን ጥያቄ መመለስ የሚያስችል ቁመና ላይ ለመድረስ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል፡፡መድረኩ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚካሄድ ሲሆን ÷የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ በጠንካራ የአመራር ቁመና ለመምራት በሚያስችል ስምምነት ላይ ይደረሳል ተብሏል።በመድረኩ ከርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተጨማሪ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች መገኘታቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።