ሩሲያ ክሪሚያን ወደ ግዛቷ የጠቀለለችው ከ10 አመት በፊት ነበር
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር፣ የሩሲያ አየር ኃይል የዩክሬን ጦር ያስወነጨፋቸውን 10 የረጅም ርቀት ሚሳይሎች ማክሸፉን አስታውቋል
ሩሲያ ወደ ክሪሚያ የተወነጨፉ 10 ሚሳይሎችን አከሸፍኩ አለች።
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር፣ የሩሲያ አየር ኃይል የዩክሬን ጦር ወደ ክሪሚያ ያስወነጨፋቸውን 10 ኤቲኤሲኤምኤስ የተባሉ የረጅም ርቀት ሚሳይሎች በዛሬው እለት ማክሸፉን አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ በቴሌግራም ገጹ ባወጣው መግለጫ በተወነጨፉት ሚሳይሎች የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ አልጠቀሰም፤ ነገርግን በሩሲያ የተሾሙት የክሪሚያዋ የወደብ ከተማ ሴቫስቶፖል አስተዳደሪ የሚሳይሎቹ ስብርባሪ መኖሪያ ቤቶች ላይ መውደቃቸውን ተናግረዋል።
Al-Ain
More Stories
ሩሲያ በዩክሬን የኢነርጂ መሰረተ ልማት ተቋማት ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት ለማቆም ተስማማች
አሜሪካ በየመን የሀውቲ ታጣቂዎች ላይ አዲስ የአየር ጥቃት መፈጸሟ ተገለጸ
ትራምፕ “የወንበዴ” ቡድን አባላት ናቸው ያሏቸውን ከ200 በላይ ቬንዙዌላውያን ከአሜሪካ አባረሩ