ሩሲያ ክሪሚያን ወደ ግዛቷ የጠቀለለችው ከ10 አመት በፊት ነበር
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር፣ የሩሲያ አየር ኃይል የዩክሬን ጦር ያስወነጨፋቸውን 10 የረጅም ርቀት ሚሳይሎች ማክሸፉን አስታውቋል
ሩሲያ ወደ ክሪሚያ የተወነጨፉ 10 ሚሳይሎችን አከሸፍኩ አለች።
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር፣ የሩሲያ አየር ኃይል የዩክሬን ጦር ወደ ክሪሚያ ያስወነጨፋቸውን 10 ኤቲኤሲኤምኤስ የተባሉ የረጅም ርቀት ሚሳይሎች በዛሬው እለት ማክሸፉን አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ በቴሌግራም ገጹ ባወጣው መግለጫ በተወነጨፉት ሚሳይሎች የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ አልጠቀሰም፤ ነገርግን በሩሲያ የተሾሙት የክሪሚያዋ የወደብ ከተማ ሴቫስቶፖል አስተዳደሪ የሚሳይሎቹ ስብርባሪ መኖሪያ ቤቶች ላይ መውደቃቸውን ተናግረዋል።
Al-Ain
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት ጉዳይ ንግግር ለመጀመር አጥጋቢ እቅድ እንዳልደረሳት ገለጸች