በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የተጣበቁ መንታ ህፃናት ተወለዱበአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የፅንስና ማህፀን ስፔሻሊስት ዶክተር አረጋኸኝ ሙሉጌታ ህፃናቱ ሁለት ጭንቅላት፣ አራት እጅ፣ አራት እግር ያላቸው ሲሆን የጋራ የሆነ አንድ ልብና አንድ እትብት እንዳላቸው አስረድተው ሁለቱም ጾታቸው ወንድ መሆኑን ተናግረዋል።ለምርመራ ወደ ሆስፒታሉ ከመጡበት 8ኛ ወር ጀምሮ ክትትል ሲደረግላቸው የቆዩት እናት በቀዶ ጥገና በሠላም መገላገላቸው ተገልጿል።እንደዚህ አይነት ክስተቶች አልፎ አልፎ የሚከሰቱ መሆናቸውን ገልፀው እናቶች የእርግዝና ምርመራ በወቅቱና በአግባቡ ቢያደርጉ ችግሩ ሊፈታ የሚችልበትም አጋጣሚ አለ ብለዋል፡፡ከሆስፒታሉ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በአሁኑ ሰአትህጻናቱ እና እናታቸው በጥሩ የጤንነት ሁኔታ ላይ ይገኛሉ፡፡
SRTA
More Stories
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከእንግሊዝ መንግሥት የ12 አምቡላንሶች ድጋፍ ተረከበ
የጥርስን ጤና መጠበቅ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት። የጥርሳችንን ንፅህና መጠበቅ መልካም የአፍ ጠረን እንዲኖረን ከማድረጉ ባለፈ የድድ እና ከአፍ ጋር በተገናኘ የሚፈጠሩ በሽታዎችን እንደሚከላከል የጥርስ ሀኪሞችን አናግሮ ሲኤንኤን ዘግቧል።
የጤና ሚኒስቴር እና ብሔራዊ መታወቂያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ