
ሃማስ ወታደራዊ ክንፍ ከወደ ራፋህ የሮኬት ጥቃት መፈጸሙም ተገልጿል 300 ሺህ የሚጠጉ ፍልስጤማውያን ከምስራቃዊ ራፋህ መውጣታቸውን የእስራኤል ጦር አስታወቀ።ጦሩ በዛሬው እለት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መግለጫ፥ ፍልስጤማውያኑ ወደ “አል ማዋሲ” እና ሌሎች ጊዜያዊ ማረፊያዎች እያቀኑ መሆኑን ጠቁሟል።ከሰኞ ጀምሮ ፍልስጤማውያን ከራፋህ እንዲወጡ የሚጠይቁ ጽሁፎችን ከአውሮፕላኖች ላይ የበተነችው እስራኤል፥ ከራፋህ ባሻገር ንጹሃን የሃማስ ታጣቂዎች መሽገውባቸዋል ካለቻቸው የጃባሊያ የስደተኞች ጣቢያ እና ከሌሎች 11 አካባቢዎች እንዲወጡም አሳስባለች።
Al-Ain
More Stories
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ
ሩሲያ በዩክሬን የኢነርጂ መሰረተ ልማት ተቋማት ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት ለማቆም ተስማማች
አሜሪካ በየመን የሀውቲ ታጣቂዎች ላይ አዲስ የአየር ጥቃት መፈጸሟ ተገለጸ