July 7, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

እስራኤል 300 ሺህ የሚጠጉ ፍልስጤማውያን ከራፋህ መውጣታቸውን ገለጸች

ሃማስ ወታደራዊ ክንፍ ከወደ ራፋህ የሮኬት ጥቃት መፈጸሙም ተገልጿል 300 ሺህ የሚጠጉ ፍልስጤማውያን ከምስራቃዊ ራፋህ መውጣታቸውን የእስራኤል ጦር አስታወቀ።ጦሩ በዛሬው እለት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መግለጫ፥ ፍልስጤማውያኑ ወደ “አል ማዋሲ” እና ሌሎች ጊዜያዊ ማረፊያዎች እያቀኑ መሆኑን ጠቁሟል።ከሰኞ ጀምሮ ፍልስጤማውያን ከራፋህ እንዲወጡ የሚጠይቁ ጽሁፎችን ከአውሮፕላኖች ላይ የበተነችው እስራኤል፥ ከራፋህ ባሻገር ንጹሃን የሃማስ ታጣቂዎች መሽገውባቸዋል ካለቻቸው የጃባሊያ የስደተኞች ጣቢያ እና ከሌሎች 11 አካባቢዎች እንዲወጡም አሳስባለች።

Al-Ain