July 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ሪያል ማድሪድ ለአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ አለፈ

በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ ሪያል ማድሪድ ባየር ሙኒክን 2 ለ1 አሸንፏል።

ሪያል ማድሪድ ባየርሙኒክን በድምር ውጤት 4 ለ 3 በማሸነፍ ለቻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ አልፏል።

ለሪያል ማድሪድ ሁለቱንም ግቦች ባለቀ ደቂቃ ተቀይሮ የገባው ሆሴሉ ሲያስቆጥር፤ ባየር ሙኒክን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ አልፎንሶ ዴቪስ አስቆጥረዋል።

ውጤቱን ተከትሎ ሪያል ማድሪድ እና ቦርሲያ ዶርትመንድ በዌምብሌይ ስታዲየም የፍፃሜ ጨዋታቸውን ግንቦት 24 ቀን 2016 ዓ.ም ያደርጋሉ።

EBC