
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኦሮሞ ሕዝብ ያገኘውን ለውጥ በማስቀጠል ሠላሙን መጠበቅና አንድነቱን ማጽናት እንዳለበት አስገነዘቡ፡፡
ከአራቱም የወለጋ ዞኖች የተውጣጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ሀገራዊ ለውጡን የሚደግፍ ሰልፍ በነቀምቴ ከተማ ወለጋ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሕዝባዊ የድጋፍ መድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር÷ ሠላም፣ አንድነትና የኢኮኖሚ ነጻነትን ማረጋገጥ ላይ ያተኮሩ ሐሳቦችን አንስተዋል::
የኦሮሞ ሕዝብ ያገኘውን ለውጥ በማስቀጠል ሠላሙን መጠበቅና አንድነቱን ማጽናት እንዳለበትም ገልጸዋል፡፡
በአካባቢው የተገኘውን ሠላም ኅብረተሠቡ ማስቀጠል እንደሚኖርበት ማስገንዘባቸውንም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።