July 2, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ለሶስት አመት በወታደራዊ አገዛዝ የቆየችው ቻድ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እያካሄደች ነው

የሽግግር ፕሬዝዳንቱ ማሃማት ኢድሪስ ዴቢ በምርጫው የማሸነፍ ቅድመ ግምት ተሰጥቷቸዋል

ነዳጅ ሻጯ ሀገር በ1960 ከፈረንሳይ ነጻነቷን ካወጀች ወዲህ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አልቻለችም

ቻድ ለሶስት አመት ከቆየችበት ወታደራዊ አገዛዝ ለመውጣት ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እያካሄደች ነው።

የመካከለኛው አፍሪካዋን ሀገር ለ30 አመት የመሩት ኢድሪስ ዴቢ በ2021 በአውደ ውጊያ ላይ ህይወታቸው ካለፈ በኋላ ልጃቸው ጀነራል ማህማት ኢድሪስ ዴቢ የሽግግር ጊዜ ፕሬዝዳንት ሆኖ በማገልገል ላይ መሆኑ ይታወቃል።

ጀነራል ማህማት በዛሬው እለት እየተካሄደ በሚገኘው ምርጫ እየተፎካከሩ ሲሆን፥ የማሸነፍም ቅድመ ግምት ተሰጥቷቸዋል።

8 ነጥብ 5 ሚሊየን መራጮች ድምጽ ለመስጠት በተመዘገቡበት ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ሱኬስ ማስራ የዴቢ ዋነኛ ተቀናቃኝ እንደሚሆኑም ነው ፍራንስ 24 ያስነበበው።

10 የሀገሪቱ ፖለቲከኞች በፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ላይ እንዳይሳተፉ የሀገሪቱ የህገመንግስት ጉዳዮች ምክርቤት መወሰኑ የሚታወስ ነው።

AL-AIN