July 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ፑቲን ታክቲካል የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ልምምድ እንዲደረግ ትዕዛዝ ሰጡ

የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ታክቲካል (ስልታዊ) የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ልምምድ እንዲደረግ ለሀገሪቱ ጦር ትዕዛዝ መስጠታቸው ተሰምቷል፡፡ልምምዱ አንዳንድ ምዕራባውያን ባለስልጣናት የሚሰነዘሩትን ጠብ አጫሪ መግለጫ እና ዛቻ ተከትሎ የሚካሄድ መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው÷ትዕዛዙን ተከትሎ ሩሲያ ታክቲካል የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎቿን የማድረግ አቅም በቅርቡ መፈተሽ ትጀምራለች፡፡በልምምዱ የደቡብ ወታደራዊ ዲስትሪክት ሚሳኤል ሃይሎች፣ ወታደራዊ አውሮፕላኖች እና የሩሲያ የባህር ኃይል እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡ልምምዱ ስልታዊ የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን አቅም ለመፈተሽ እና በተመረጡ ቦታዎች ለማሰማራት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ፕሬዚዳንት ፑቲን÷ ሩሲያ የግዛት አንደነቷንና ሉዓላዊነቷን ለማስጠበቅ የሀገሪቱ ጦር በተጠንቀቅ ላይ እንደሚገኝ ማረጋገጣቸውንም አር ቲ ዘግቧል፡፡

FBC