July 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አሜሪካ የአልቃይዳ መሪ ነው በሚል ገድየዋለሁ ያለችው ሰው ድሃ ገበሬ ሆኖ ተገኘ

የአሜሪካ አየር ሀይል በሶሪያ ቁልፍ የአልቃይዳ መሪ ነው በሚል የተገደለው ሰው በመጨረሻም ዶሮ አርቢ ሆኖ መገኘቱን አረጋግጫለሁ ብላለች

የአሜሪካ አየር ሀይል በሶሪያ ቁልፍ የአልቃይዳ መሪ ነው በሚል የተገደለው ሰው በመጨረሻም ዶሮ አርቢ ሆኖ መገኘቱን አረጋግጫለሁ ብላለች

የአልቃይዳ መሪ ነው በሚል በስህተት በአሜሪካ ጦር የተገደለው ሰው የ60 ዓመት ሶሪያዊ አርሶ አደር ነበር

አሜሪካ የአልቃይዳ መሪ ነው በሚል ገድየዋለሁ ያለችው ድሃ ገበሬ ሆኖ ተገኘ፡፡

የአሜሪካ አየር ሀይል ጦር በሶሪያ የሚንቀሳቀሰው አልቃይዳ ቁልፍ አመራር ነው በሚል ነበር የድሮን ጥቃት የፈጸመው፡፡

ጥቃቱም ውጤታማ እንደነበር እና የአልቃይዳ አመራር መገደሉንም ሀገሪቱ አስታውቆም ነበር፡፡

ባሳለፍነው ግንቦት ወር ላይ እንደተፈጸመ የተገለጸው ይህ ጥቃት ኢላማውን እንደሳተ እና በዶሮ እርባታ የሚተዳደር አርሶ አደር ስለመገደሉ በወቅቱ የሟች ቤተሰቦች ተናግረዋል፡፡

ይህ ጥቆማ የደረሰው የአሜሪካ አማዕከላዊ እዝም ባደረገው ማጣራት በወቅቱ በተፈጸመው ጥቃት የተባለው የአልቃይዳ መሪ ሳይሆን ሉፍቲ ሀሰን ማስቶ የተሰኘ ዶሮ አርቢ አርሶ አደር እንደተገደለ ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡

የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ ይፋ ባደረገው ምርመራ የ60 ዓመቱ አዛውንት በተፈጸመው የድሮን ጥቃት እንደተገደለ ይህም ስህተት መሆኑን አረጋግጠናልም ብሏል፡፡

በአሜሪካ የሰው አልባ አውሮፕላን ወይም ድሮን ጥቃት በስህተት የተገደለው ማስቶ ወንድም በበኩሉ ወንድሙ ዶሮ ከማርባት እና በግ ከመንዳት ውጪ ከአልቃይዳም ሆነ ከየትኛውም ቡድን ጋር ግንኙነት የሌለው ሰው ነው ብሏል፡፡

Al-Ain