
በኢትዮጵያ የነባርና የዲጂታል ሚዲያዎች መበራከት የፕሬስ ነፃነት መሰረታዊ መብት ተጠቃሚነት በአገሪቱ እያደገ ለመምጣቱ ተጨባጭ ማሳያ ነው ሲል የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።
የዓለም የፕሬስ ነፃነት ቀንን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ የሚገኙ አንዳንድ ኤምባሲዎች የሰጡትን የጋራ መግለጫ መመልከቱን የጠቀሰው ሚኒስቴሩ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የፕሬስ ነፃነት እንዲከበር ፅኑ አቋም አለው ብሏል።
ይህ መብት ሊተገበር እና ሊጠበቅ የሚገባው ደግሞ በሕግ የበላይነት ማዕቀፍ ውስጥ እንደሆነ ይታወቃል ነው ያለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው።
በኢትዮጵያ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የነባር እና የዲጂታል ሚዲያዎች ቁጥር መብዛትም የዚህ መሰረታዊ መብት ተጠቃሚነት በአገሪቱ እያደገ ለመምጣቱ ተጨባጭ ማሳያ እንደሆነም መግለጫው ጠቅሷል።
ኢትዮጵያ ከአጋሮቿ እና ሁሉም ባለድርሻ አካላት በኩል ገንቢ ግንኙነትን ትቀበላለች ብሏል የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው።
ሆኖም በተደጋጋሚ በተለያዩ ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ በመሰባሰብ በደቦ የሚወጡ መግለጫዎች ለሁለትዮሽ ግንኙነት የማይጠቅሙ እንዲሁም ከተለመደውና ቅቡልነት ካለው በሁለትዮሽ የዲፕሎማሲያዊ ስምምነት ከተመሠረተው ግንኙነት ደንቦችና አሰራሮች ጋር የሚጣረሱ መሆኑን ሚኒስቴር መ/ቤቱ ገልጿል።
EBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።