![](https://www.mashafm.gov.et/wp-content/uploads/2024/05/438170136_746497041005719_7395330779324781155_n.jpg)
በአሸባሪው ሸኔ ታጣቂዎች ላይ የሚወሰደው የማያዳግም ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሰለሞን ኢተፋ ገለጹ።
የሽብር ቡድኑን በመደምሰስ በአንዳንድ አካባቢዎች የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ከምንጩ ለማድረቅ የሚያስችል ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
በጥናት ላይ የተመሰረቱ በርካታ ዘመቻዎችን በማድረግ የአሸባሪ ቡድኑን አባላት በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን እና በቡድኑ ታጣቂዎች ላይ የሚወሰደው የማያዳግም ርምጃም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡
በተከናወኑ ሕግ የማስከበር ሥራዎች ሠላም እንዲረጋገጥ ማድረግ ተችሏል ማለታቸውን ከመከላከያ ሠራዊት ማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
ኢትዮጵያ የፊታችን ነሀሴ በአንካራ በሚካሄደው ድርድር ምን ትጠብቃለች?
የአይቻልም እና የአይሆንም መንፈስን መስበር ከተቻለ የማይቻል ነገር የለም “- ተማሪ ወጋየሁ ወራጆ
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ለምክር ቤቱ ማብራሪያ ይሰጣሉ