July 7, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

በአሸባሪው ሸኔ ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል- የደቡብ ዕዝ

ሌተናል ጄኔራል ሰለሞን ኢተፋ

በአሸባሪው ሸኔ ታጣቂዎች ላይ የሚወሰደው የማያዳግም ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሰለሞን ኢተፋ ገለጹ።

የሽብር ቡድኑን በመደምሰስ በአንዳንድ አካባቢዎች የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ከምንጩ ለማድረቅ የሚያስችል ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

በጥናት ላይ የተመሰረቱ በርካታ ዘመቻዎችን በማድረግ የአሸባሪ ቡድኑን አባላት በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን እና በቡድኑ ታጣቂዎች ላይ የሚወሰደው የማያዳግም ርምጃም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

በተከናወኑ ሕግ የማስከበር ሥራዎች ሠላም እንዲረጋገጥ ማድረግ ተችሏል ማለታቸውን ከመከላከያ ሠራዊት ማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

FBC